ETC News    
   
     WHO IS WHO
     CHECK MAIL
     VACANCY
     YELLOW PAGES
     FEEDBACK
     FAQs
 
Dialing Codes
   
Interurban Dialing Code
  Essential Numbers
  International Dialing Codes
 
Websites at Ethiopage
   
 
 
 
  ኮርፖሬሽኑ የሞባይል ደንበኞች የሞባይል ኢንተርኔት GPRS አገልግሎትን በነጻ ማስጀመር እንዲችሉ አደረገ፡፡
July 12, 2010

የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን የሞባይል ኔትወርክን በመጠቀም የድምፅ፣ የተንቀሳቃሽ ምስል እና የፅሁፍ መልዕክቶችን ለመቀበልና ለማስተላለፍ የሚያስችለው የሞባይል ኢንተርኔት ወይም የGPRS አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የኔትወርክ ማስፋፋት ሥራ ተጠናቆ በአሁኑ ወቅት 2.146 ሚሊዮን ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል አቅም ተፈጥሯል፡፡ በመሆኑም ሁሉም የድህረ እና የቅድመ ክፍያ የሞባይል ተጠቃሚዎች አገልግሎቱን በነጻ ማስጀመር ወይም activate ማድረግ እንዲችሉ ተደርጓል፡፡  

ሆኖም የGPRS አገልግሎትን ለማግኘት ደንበኞች የ2G እና ከዚያ በላይ የሆነ የሞባይል ቀፎ ሊኖራቸው የሚገባ ሲሆን ቀፎዎቹ ውስጥ ኮንፊገር ለማድረግ የሚያስችሉት APN ወይም የWAP ምርጫ ሊኖራቸው ይገባል፡፡

 የጂፒ አር ኤስ አገልግሎትን በሞባይል ቀፎ ላይ ለማግኘትና ለመጠቀም
 ወይም configure ማድረግን በተመለከተ፡-

የGPRS አገልግሎትን ለማግኘት ሁለት ዓይነት የሞባይል ቀፎ አጠቃቀም configuration መንገዶች አሉ፡- እነሱም፡-

1. የደንበኛው የሞባይል ቀፎ Access Point Name ካለው etc.com የሚለውን በማስገባት የGPRS አገልግሎትን ማስጀመር /activate/ ማድረግ፣
2.    የደንበኛው የሞባይል ቀፎ APN ሳይሆን WAP ከሆነ “የWAP አገልግሎት ሰጪ” የሚለው አድራሻ ላይ በማስገባት የGPRS አገልግሎትን ማስጀመር activate ማድረግ ይቻላል፡፡

የጂፒ አር ኤስ አገልግሎት አጠቃቀም GPRS configuration በተለያዩ የሞባይል ቀፎዎች ላይ የተለያየ ሲሆን፣ የሚከተሉትን አራት ዓይነት የሞባይል ቀፎዎችን በምሳሌ በማስቀመጥ የአገልግሎቱን አጠቃቀም ማየት ይቻላል፡፡  

1ኛ. በሶኒ ኤሬክሰን Sony Ericsson የሞባይል ቀፎ


2ኛ. በኖኪያ Nokia-Series ሞባይል ቀፎ አጠቃቀምን በተመለከተ፡-


3ኛ. በሳጌም Sagem OT 290 የሞባይል ቀፎ አጠቃቀምን በተመለከተ፡-


4ኛ. በሳምሰንግ Samsung ሞባይል ቀፎ አጠቃቀምን በተመለከተ፡-



የGPRS አገልግሎት ተጠቃሚዎች ሊያውቋቸው የሚገቡ ተጨማሪ ጉዳዮች
   
•    የGPRS አገልግሎትን የሞባይል ስልክ ቁጥር በማስገባት አይሠራም፤ በምትኩ የአክሰስ ፓይንት ኖድ APN ይጠቀማል፡፡
•    የአከፋፈል ሥርዓቱ በጊዜ ቆይታ per minute ሳይሆን ደንበኞች በላኩት እና በተቀበሉት የዳታ መጠን በኪሎ ባይት ተሰልቶ የሚከፈል ሲሆን ለ100 ኪሎ ባይት 4አራት ሳንቲም እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡
•    የGPRS አገልግሎት በዋየርለስ አክሰስ ኘሮቶኮል WAP አማካይነት ዳታዎች ለማስተላለፍ የሚያስችል ነው፡፡
•    የGPRS አገልግሎት ፍጥነት በተለያዩ ጉዳዮች የሚጨምር እና የሚቀንስ ቢሆንም ለአንድ ደንበኛ ሲሰጥ ከፍተኛው እስከ 21.4 kbs ድረስ አቅም ያለው ዳታ የማስተላለፍ ብቃት ይኖረዋል፡፡  
•    የGPRS አገልግሎትን ለመጠቀም ደንበኞች የሚጠቀሙበት የሞባይል ቀፎ ይህን አገልግሎት ሊሠጥ የሚችል GPRS enabled የሆነ የቀፎ ዓይነት መሆን ይኖርበታል፡፡

የGPRS አገልግሎት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮች እና መፍትሔዎችን በተመለከተ፡-
   
1.የአገልግሎት መቋረጥ በሚያጋጥምበት ጊዜ
     
•    ሲም ካርዱ ለዳታ አገልግሎት ዝግጁ መደረጉን ማረጋገጥ እና በGPRS አማካኝነት ለሚደረግ ግንኙነት ተገልጋዩ አካውንቱ ዝግጁ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት፡፡

2. የተሳሳተ አገልግሎት አጠቃቀም በሚያጋጥምበት ጊዜ፡-

•    ኢ-ሜይል መቀበል ነገር ግን መላክ የማያስችል ሁኔታ የሚያጋጥመው ተገልጋዩ የተሳሳተ የጂፒ አር ኤስ አክሰስ ፓይንት ሲጠቀም ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ የጂፒ አር ኤስ መቀበያዎች ከአገልግሎት ሰጪው ኔትወርክ መውጫና መግቢያ ጋር እንዲገናኙ ተደርጎ በ“WAP” የሚሰሩ ናቸው፡፡ ይህ አሠራርም  ከመደበኛው የኢንተርኔት ድረገጽ ውጪ አስፈላጊ የዜና ይዘት ያላቸውን ገጾች ተገልጋዩ ፈልጎ browse ለማግኘት የሚያስችለው ሲሆን የመደበኛውን ኢንተርኔት አገልግሎት ሲፈለግ ግን የጂፒ አር ኤስ መቀበያውን ከኢንተርኔት ኤ ፒ ኤን APN ኔትወርክ ጋር እንዲገናኝ ማስተካከል ያስፈልጋል፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0116612997 ደውለው ይጠይቁ፡፡


Ethiopian Telecommunications Corporations
 
 
 
 
 
 
 
 
Copyright© 2009 Ethiopian Telecommunications Corp. All rights reserved!